Kidus Asnake Law Office

Kidus Asnake Law Office Every person equal B 4 the law

17/09/2023

በወንጀል የተከሰሰ ሰው ሊቀጣ የሚችለው ወይም ፍርድ ሊጣልበት የሚችለው የቀረበበት ክስ በከሳሽ ፍጹም ከጥርጣሬ ውጪ በሆነ ማስረጃ Beyond a Reasonable Doubt ) ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
ያለ አንዳች ጥርጣሬ ይህ አንድን ሰው በወንጀል ጥፋተኛ ለማድረግ የሚጠየቅ
የማስረጃ ደረጃ ነው፡፡ ዓቃቤ ህግ ተከሳሹ ጥፋቱን ስለመፈጸሙ ያለ አንዳች ጥርጣሬ ምሉዕ የሆነ ማስረጃ
ያለው መሆኑን ለችሎት ማስረዳት አለበት፡፡

10/09/2023

የተከበሩት ዳኛ በጥቁሩ ካባቸው ደምቀው በችሎት አስከባሪ ፖሊስ ታጅበው ወደ ችሎት ሲገቡ ፖሊሱ ገና “አንዴ ተነሱ!” ብሎ ተናግሮ ሳይጨርስ በአዳራሽ የነበረው ሁሉ ብድግ ብሎ አከበራቸው፡፡ “ተቀመጡ!” አሉና የመጀመሪያውን መዝገብ ገልጠው ከሳሽና ተከሳሽን ተጣሩ፡፡ በመቀጠል የግራ ቀኙ ጠበቆች ብድግ ብለው በየተራ ስማቸውን አስመዘገቡ፡፡

ዳኛው በችሎት አዳራሽ የተሰበሰበውን ባለጉዳይ አንዴ አየት አደረጉና ወደ ጠበቆቹ ዞረው በትኩረት እየተመለከቱ “በዚህ ጉዳይ የከሳሽና የተከሳሽ ጠበቆች የሰጣችሁን ጉቦ ደርሶኛል” በማለት ተናገሩ፡፡ ይሄኔ ጠበቆቹ በሐፍረት እርስ በእርስ መተያየት ጀመሩ፡፡

“የከሳሽ ጠበቃ የሰጠኝ 15 ሺ ብር ሲሆን የተከሳሽ ጠበቃ ደግሞ 10 ሺ ብር ሰጥቶኛል፡፡” ዳኛው ይህን ከተናገሩ በኋላ ከኪሳቸው ቼክ አውጥተው ለከሳሽ ጠበቃ የሚከፈል 5 ሺ ብር ከጻፉ በኋላ “የከሳሽ ጠበቃ 5 ሺ ብር እላፊ ሰጥተኸኛል፡፡ እንካ ቼኩን ተቀበል፡፡” ብለው ቼኩን ሰጡት፡፡ ጠበቃው እያላበው ቼኩን ተቀበለ፡፡

በመጨረሻም ዳኛው ፊታቸው ላይ እፎይታና እርጋታ እየተነበበ እንዲህ አሉ፡፡

“አሁን ችሎቱ የእናንተን ጉዳይ ያለ አድልዎ ገለልተኛ ሆኖ ማየቱን ይቀጥላል፡፡”

05/09/2023

EVERY PERSON EQUAL B 4 THE LAW

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00

Telephone

+251955424370

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kidus Asnake Law Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share