01/05/2026
⚖️ የመዝገብ ቁጥር፦ 234500 ⚖️
ወደ ከተማ ተካልሎ ነገር ግን የከተማ ፕላን ባልተሰራበተ አከባቢ የተሰራን ቤት አስተዳደሩ ካፈረሰ የሁከት ተግባር ነው።
አንድ የክፍለ ከተማ አስተዳደር "የግንባታ ፈቃድ የላችሁም፣ ግንባታው ህገ-ወጥ ነው" በሚል የዜጎችን ቤት ለማፍረስ ሙከራ ያደርጋል። ይሁን እንጂ ይዞታው ገና ከገጠር መሬት አስተዳደር ወደ ከተማ መሬት ሙሉ በሙሉ ያልተሸጋገረ እና በገጠር ይዞታነት የሚታወቅ ነበር።
የሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ትርጉም
ፍርድ ቤቱ የክፍለ ከተማውን ክርክር ውድቅ በማድረግ የሚከተሉትን ነጥቦች አፅንቷል፦
✅ ህጉ ምን ይላል? መሬቱ በገጠር ይዞታነት እስከታወቀ ድረስ፣ የከተማ ግንባታ አዋጅ (ቁጥር 624/2001) በዝምታ ተፈፃሚ አይሆንም።
✅ መብታችሁ፡ አንድ አርሶ አደር ወይም የገጠር መሬት ባለይዞታ ለራሱና ለቤተሰቡ መጠለያ የሚሆን ቤት በይዞታው ላይ የመስራት መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
✅ የአስተዳደሩ ስልጣን ገደብ፡ መሬቱ በይፋ ወደ ከተማ መሬት አስተዳደር ሳይዞር እና የከተማ መዋቅራዊ ፕላን ሳይዘጋጅለት፣ አስተዳደሩ "ፈቃድ የላችሁም" በሚል የግንባታ እገዳ ወይም ማፍረስ አይችልም። እንዲህ አይነት ተግባር "የሁከት ተግባር" ነዉ ተብሎ ተወስኗል ።