ፍቃዱ ሞላ የህግ ቢሮ Fekadu Molla Law Office

ፍቃዱ ሞላ የህግ ቢሮ Fekadu Molla Law Office ከሰማይ በታች ህግ የማይመለከተው ነገር የለም።

⚖️  የመዝገብ ቁጥር፦ 234500 ⚖️ ወደ ከተማ ተካልሎ ነገር ግን የከተማ ፕላን ባልተሰራበተ አከባቢ የተሰራን ቤት አስተዳደሩ ካፈረሰ የሁከት ተግባር ነው።አንድ የክፍለ ከተማ አስተዳደር ...
01/05/2026

⚖️ የመዝገብ ቁጥር፦ 234500 ⚖️
ወደ ከተማ ተካልሎ ነገር ግን የከተማ ፕላን ባልተሰራበተ አከባቢ የተሰራን ቤት አስተዳደሩ ካፈረሰ የሁከት ተግባር ነው።

አንድ የክፍለ ከተማ አስተዳደር "የግንባታ ፈቃድ የላችሁም፣ ግንባታው ህገ-ወጥ ነው" በሚል የዜጎችን ቤት ለማፍረስ ሙከራ ያደርጋል። ይሁን እንጂ ይዞታው ገና ከገጠር መሬት አስተዳደር ወደ ከተማ መሬት ሙሉ በሙሉ ያልተሸጋገረ እና በገጠር ይዞታነት የሚታወቅ ነበር።
​የሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ትርጉም
ፍርድ ቤቱ የክፍለ ከተማውን ክርክር ውድቅ በማድረግ የሚከተሉትን ነጥቦች አፅንቷል፦
​✅ ህጉ ምን ይላል? መሬቱ በገጠር ይዞታነት እስከታወቀ ድረስ፣ የከተማ ግንባታ አዋጅ (ቁጥር 624/2001) በዝምታ ተፈፃሚ አይሆንም።
✅ መብታችሁ፡ አንድ አርሶ አደር ወይም የገጠር መሬት ባለይዞታ ለራሱና ለቤተሰቡ መጠለያ የሚሆን ቤት በይዞታው ላይ የመስራት መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
✅ የአስተዳደሩ ስልጣን ገደብ፡ መሬቱ በይፋ ወደ ከተማ መሬት አስተዳደር ሳይዞር እና የከተማ መዋቅራዊ ፕላን ሳይዘጋጅለት፣ አስተዳደሩ "ፈቃድ የላችሁም" በሚል የግንባታ እገዳ ወይም ማፍረስ አይችልም። እንዲህ አይነት ተግባር "የሁከት ተግባር" ነዉ ተብሎ ተወስኗል ።

02/04/2026

*****አዋጅ ቁጥር 1410/2018****,
*የወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና የማስረጃ ሕግ
----------------------
(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 24፣ 2018 ዓ.ም፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ13ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና የማስረጃ ሕግ ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል፡፡

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ ሪፖርት እና የውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡

ረቂቅ ሕጉ በወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሥርዓት የወንጀል ፍርድ ሂደት የተጠርጣሪን እና የተከሳሽን እንዲሁም በወንጀል ምክንያት የተጎዱ ሰዎችን ሰብአዊ መብቶች ለማክበርና ለማስከበር የሕግ የበላይነት በማስፈን የአሰራር ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል፡፡

የተቀላጠፈ የፍትህ ሥርዓት እንዲኖር ለማስቻል እና ልዩ የወንጀል ምርመራ ዘዴን እንዲሁም ለተጎጂዎች ካሣ የሚከፈልበትን አግባብ ያካተተ ዓለም አቀፍ መርህን የተከተለ ረቂቅ ሕግ እንደሆነ የተከበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ አያይዘው አስረድተዋል፡፡

ረቂቅ ሕጉ ከኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት እና ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች፣ መርሆች እና እሴቶች እንዲሁም ከወንጀል ህጉ ጋር የተጣጣመና ዘመናዊ በመሆኑ ጠቀሚ እንደሆነ ሰብሳቢዋ ጠቁመዋል፡፡

ረቂቅ ህጉ በህገ መንግስቱ፣ በወንጀል ሕጉ፣ ዓለም አቀፍ ህጎች እና በሌሎች አግባብነት ባላቸው ህጎች የተረጋገጡ ልዩ ትኩረት ለሚያሻቸው ለሴቶች፣ ህፃናት እና አካል ጉዳተኞች የተሰጣቸውን መብቶች ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነም የተከበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ ገልጸዋል፡፡

የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው ረቂቅ አዋጁ ረጅም ጊዜ የቆየና የዘገየ ቢሆንም በህዝቡ ዘንድ የቅሬታ ምንጭ የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት ወቅቱን የሚመጥን አዋጅ በመሆኑ የህዝብን የፍትህ ሥርዓቱን ለማስፈን እንደሚያግዝ ገልጸዋል፡፡

የዜጎችን ሰብአዊ እና ዲሞክራሲአዊ መብቶችን ለማስከበር እና የፍትህ ሥርዓቱን በማዘመን ወቅቱን ያዋጅ አግልግሎት ለመስጠት ረቂቅ አዋጁ ሚናው የጎላ መሆኑን የምክር ቤት አባላት አመላክተዋል፡፡፡

በሌላ በኩል የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ በአተገባበር ሂደት ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን ታሳቢ በማድረግ ከፍትህ አካላት ጋር መወያየት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡

ከምርመራ ሂደት እና ከዲጂታል አሰራሮች ጋር በተያያዘ ዜጎችን ህገ መንግስታዊ መብትን በጠበቀ መልኩ መሆን እንዳለበት የምክር ቤት አባላቱ አስገንዝበው፤ በማረሚያ ቤት ቆይተው ፍርድ ቤት ነፃ የሚላቸው ዜጎች የካሳ ክፍያ ሥርዓትን ለመዘርጋት በግልጽ በረቂቅ አዋጁ ማስቀመጥ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ምክር ቤቱ፤ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት እና የማስረጃ ሕግ ረቂቅ አዋጅ ፤ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 አድረጎ በሁለት ተቃውሞ፤ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል፡፡

(በ-መኩሪያ ፈንታ)

09/11/2025
27/1/2018 ዓ.ምየፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጠቅላላ ጉባዔ
06/10/2025

27/1/2018 ዓ.ም
የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጠቅላላ ጉባዔ

ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህንን አድርጉ ብሏል።
01/10/2025

ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህንን አድርጉ ብሏል።

***** የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ******ጉዳዩ የዉርሰ፣ የቤተሰብ ፣ የገጠር መሬት ወዘተ ... የሚመለከት የክልል ጉዳይ ቢሆንም ተከራካሪዎች የሁለት ክልል ነዋሪዎች ከሆኑ ጉዳዪን ለማ...
22/08/2025

***** የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ******
ጉዳዩ የዉርሰ፣ የቤተሰብ ፣ የገጠር መሬት ወዘተ ... የሚመለከት የክልል ጉዳይ ቢሆንም ተከራካሪዎች የሁለት ክልል ነዋሪዎች ከሆኑ ጉዳዪን ለማየት ስልጣን ያለው የፌደራል ፍርድ ቤት ነው ።

*****የኔ እይታ*****
፨ዉሳኔዉ አሸናፊ ሀሳብ በአብላጫ ድምፅ የተሸነፈበት፣ የነገሩ ሕገመንግስታዊነት ይልቅ የአባላቱ ማንነት የጎላ ሚና የተጫወተበት ፣ የሕገመንግስት ትርጉም ጠያቂ የሆነወ የኦሮሚያ ክልል ጠ/ፍ/ቤት አዲስ አበባ በሕገመንግስቱ ክልል አለመሆኗን እና የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ መሆኗን ጠቅሶ የጠየቀው የትርጉም ጥያቄ ሆነ ተብሎ የተተወ በሚያስመስል መልኩ ምንም ትንታኔ ያልተሰጠበት ዉሳኔ ነው ።

24/10/2024

ሰላም
Saro

19/04/2022

**የፌደራል ጠበቆች ማህበር መልዕክት**
የፌዴራል ጠበቆች ምዝገባ

የፌዴራል ጠበቆች ማኅበር በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 አንቀጽ 57 ጥር 15 ቀን 2014 ዓ.ም መሠረት መቋቋሙ ይታወቃል። በመሆኑም የማናቸውም እና የመጀመሪያ ደረጃ የተሰጣቸው የፌደራል ፍ/ቤቶች ጠበቆች እንዲሁም የጥብቅና ድርጅቶች በአባልነት ያቀፈ ሲሆን ማንኛውም ጠበቃ ወይም የጥብቅና ድርጅት የጥብቅና ፍቃድ ሲሰጠው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የማኅበሩ አባል እንደሚሆን በአዋጁ በግለጽ ተደንግጎ ይገኛል። በመሆኑም የፌዴራል ጠበቆች ማኀበር በሥሩ ያሉትን ጠበቆች መመዝገብ፣ መረጃቸውን በአግባቡ መያዝ እና ማደረጃት እንዲሁም ለሌሎች አስፈላጊ አገልግሎቶች ማዘጋጀት ተቀዳሚ ተግባሩ ነው።

ስለሆነም የዚህ ምዝገባ ዓላማ በፌደራል ደረጃ የሚገኙ እና ፍቃድ የተሰጣቸው የማናቸውም እና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤቶች ጠበቆችን እና የጥብቅና ድርጅቶችን ምዝገባ በማድረግ መረጃዎቻቸውን አደራጅቶ መያዝ እንዲሁም ለአበል ጠበቆች ደረጃውን የጠበቀ መታወቂያ መስጠት ነው።

ምዝገባው የሚካሔደው በዋናነት በኦንላይን ሲሆን ይህም ጠበቆች ባሉበት ሆነው ትክክለኛ መረጃቸውን በእጃቸው በያዙት ስልክ ወይም በኮምፒወተር እንዲያስመዘግቡ ሲሆን በኦንላይን ማስመዝገብ ለማይችሉ ደግሞ በተመረጡ ሁለት ቦታዎች ማለትም በፍትሕ ሚኒስቴር ዋና መሥሪያ ቤት እና በፍትሕ ሚኒስቴር አራዳ ምድብ በአካል ተገኝተው ማስመዝገብ የሚችሉበት መንገድ ተመቻችቷል።

ምዝገባውን በኦንላይን ለማስመዝገብ ይህንን ሊንክ ይጫኑ፡

t.ly/RzWs (ይህ ሊንክ በየትኛውም ጊዜ ይሠራል)

ለምዝገባው የሚያስፈልገውን አንድ ሺ ብር በሞባይል ስልክዎ ወይም በመረጡት የሞባይል መተግበሪያ ወደማኅበሩ የሒሳብ ቁጥር ለማስገባት ይችላሉ። ያስገቡበትን ማስረጃ (ስክሪን ሾት፣ የባንክ ስሊፕ ወይም ማናቸውንም ማስረጃ) ማያያዝ ይችላሉ።

የማኅበሩ የሒሳብ ቁጥር፦ 1000469494218 (ንግድ ባንክ)

ምዝገባውን እስከ ሚያዚያ 28 ቀን 2014 ድረስ ያከናውኑ፤

ይህንን መረጃ ለሌሎች ጠበቆች ያጋሩ

Create a new survey on your own or with others at the same time. Choose from a variety of survey types and analyse results in Google Forms. Free from Google.

*****ለፌደራል ጠበቆች*****https://www.facebook.com/100064822533625/posts/352691833568232/?app=fbl
18/04/2022

*****ለፌደራል ጠበቆች*****

https://www.facebook.com/100064822533625/posts/352691833568232/?app=fbl

ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፍርድ ቤት ጠበቆች በሙሉ

በፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፈቃድ አሰጣጥና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2013 አንቀጽ 59 (1) መሰረት የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባዔ ተጠርቶ የአመራር አባላት ተመርጠው ወደ ስራ የተገባ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በአዋጁ አንቀጽ 57 (4) መሰረት ማንኛውም ጠበቃ ወይም የጥብቅና ድርጅት የጥብቅና ፈቃድ ሲሰጠው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የማህበሩ አባል እንደሚሆን የተደነገገ በመሆኑ ለማህበሩ አባልነት ምዝገባ ብር 1000 (አንድ ሺህ) በኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ስም በተከፈተው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000469494218 ገቢ በማድረግ የገቢ ደረሰኙን SLIP በማቅረብ በአካል ባምቢስ በሚገኘው የፍትሕ ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤት ወይም አራዳ የፍትሕ አካላት ህንጻ 9ኛ ፎችቅ በሚገኘው የማህበሩ ቢሮ በመቅረብ ምዝገባ ማከናወን የሚገባችሁ ሲሆን በአካል መቅረብ የማትችሉ በኦንላይን ከዚህ በታች በተመለከተው የዌብ አድራሻ በመጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

https://www.eag.gov.et/am-et/አገልግሎታችን
ማሳሰቢያ፡-
• ምዝገባው የሚካሄደው በፍትህ ሚኒስቴር ዋናው መስሪያ ቤት ባለው ቢሮ እና አራዳ በሚገኘው የፍትሕ አካላት ህንጻ 9ኛ ፎች የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ቢሮ ብቻ ነው፤
• ምዝገባው የሚካሄደው ከሚያዝያ 7 ቀን እስከ ሚያዝያ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ብቻ ነው፤
• በኦን ላይን ሲመዘገቡ የጥብቅና ፍቃድ ደብተራችሁ ፎቶዎቹ የሚገኝበትን ገጽ እና የመጨረሻ የታደሰበትን ገጽ ስካን በማድረግ ማያያዝ ይኖርባችኋል፣
• ለምዝገባ ክፍያ ገቢ ተደረገበት ደረሰኝ በኦን ላይን መያያዝ ሲኖርበት በአካል ለሚደረግ ምዝገባ ደግሞ ኮፒው መቅረብ ይኖርበታል፣
• እስከ ሚያዝያ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ያልተመዘገበ ማንኛውም ጠበቃ የማህበሩ አባል እንዳልሆነ ተቆጥሮ የጥብቅና አገልግሎት ከመስጠት ይታገዳል፣

የፍትሕ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ሚያዝያ 7 ቀን 2014 ዓ.ም

***ጊዜ ቀጠሮ፤ ምንነት፣አስፈላጊነት...***https://www.facebook.com/100064822533625/posts/346414377529311/?app=fbl
05/04/2022

***ጊዜ ቀጠሮ፤ ምንነት፣አስፈላጊነት...***

https://www.facebook.com/100064822533625/posts/346414377529311/?app=fbl

የጊዜ ቀጠሮ ምንነት እና የፖሊሰ፣ የዐቃቤ ሕግና የፍርድ ቤት ሚና!

ሰላም ጤና ይስጥልን የፍትህ ሚኒስቴር የማህበራዊ ሚዲያ ተከታዬቻችን እንደምን አላችሁ! ዛሬ የጊዜ ቀጠሮ ምንነት እና የፖሊሰ የዐቃቤ ሕግና የፍርድ ቤት ሚና በሚል አርእስት አንድ አጠር ያለ ፅሁፍ ወደናንተ ልናደርስ ወደናል! በፅሁፋችን የጊዜ ቀጠሮ ምንነት፣የጊዜ ቀጠሮ አላማ፣የጊዜ ቀጠሮ ርዝማኔና መሰል ተያያዥ ጉዳዮች የሚዳሰሱ ሲሆን ፅሁፉን በፍትህ ሚኒስቴር የንቃተ ህግ፣ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ የሆኑትን አቶ አበበ ጌታሁን አነጋግረን አዘጋጅተንላኋል፤አንብባችሁ ንቃተ ህጋችሁን ከፍ ታደርጉበትና ታተርፉበት ዘንድ ጋብዘናችኋል፡፡

ወንጀል በተለያዩ ምክንያቶች በቸልተኝነት ወይም ሆን ተብሎ ሊፈጸም ይችላል፡፡ አንድ ወንጀል ተፈጽሞ ሲገኝ ፖሊስ ወንጀሉ በተፈጸመበት ስፍራ በመድረስ ወንጀል ፈጻሚውን የመለየት ስራ ያከናውናል፡፡ የወንጀል ድርጊቱን ፈጽመሀል ተብሎ ተጠርጥሮ የተያዘ ሰው በአርባ ስምንት ሰአት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለበት የኢ.ፌ.ድ.ሪ ሀገ-መንግስት አንቀጽ 19 እና የወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርአት ህግ አንቀጽ 59 ላይ በግልጽ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ አንድ ተጠርጣሪ ፍርድ ቤት ከቀረበ በኋላ ፍርድ ቤቱ በእስር እንዲቆይ ወይም በዋስትና እንዲለቀቅ ውሳኔ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ ተጠርጣሪው በእስር እንዲቆይ ውሳኔ ሲሰጥ በሁለት ምክንያቶች ሲሆን እነዚህም አንደኛ የተጠረጠረበት ወንጀል ዋስትና የሚከለክል ሲሆንና ሁለተኛ ደግሞ ፖሊስ ምርመራውን ባለመጨረሱ ምክንያት ተጨማሪ የምርመራ ቀን እንዲሰጠው ሲጠይቅ ብቻ ነው፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍም ለፖሊስ የሚሰጠው ተጨማሪ ጊዜ ምንነትና የዐቃቤ ሕግና የፍርድ ቤት ሚና ምንድን ነው የሚሉትን ጉዳዮች ይዳሰሳሉ፡፡

የጊዜ ቀጠሮ ምንነት፡-

የጊዜ ቀጠሮ ትርጉሙ በቀጥታ በየትኛውም ህግ ላይ የተቀመጠ ባይሆንም በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርአት ህግ ቁጥር 59 ላይ የተቀመጠውን በመመልከት ትርጉም መስጠት ይቻላል። ከላይ በተገለጸው አንቀጽ ላይ እንደተቀመጠዉ አንድ በወንጀል ተጠርጥሮ የተያዘ ሰው በዐቃቤ ሕግ በኩል የወንጀል ክስ ከመቅረቡ በፊት በወንጀል ምርመራ ወቅት ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት ቀርቦ መርማሪ ፖሊስ ምርመራውን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ጊዜ እዲሰጠውና ምርመራውን እስኪጨርስ ተጠርጣሪው ማረፊያ ቤት እንዲቆይ ሲጠይቅ ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪው ምርመራው እሰኪያልቅ ድረስ ለተወሰነ ጊዜ ማረፊያ ቤት እንዲቆይ የሚደረግበት ስነ ስርአት የጊዜ ቀጠሮ ይባላል።

የጊዜ ቀጠሮ አላማ፡-

ማንኛውም የተያዘ ሰው ፍርድ ቤት ቀርቦ በዋስትና የመፈታት መብት እንዳለው በኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገ-መንግስት የተረጋገጠ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ ዋስትና የሚከለከልበት ሁኔታ አለ፡፡ የጊዜ ቀጠሮ ዋና አላማው ፖሊስ በተጠርጣሪው ላይ የሚያካሂደውን ምርመራ ባለማጠናቀቁ ተጨማሪ ጊዜ ተሰጥቶት ምርመራውን በተገቢ ሁኔታ ማጣራት እንዲችል ማድረግ ነው፡፡ በሌላ በኩል የጊዜ ቀጠሮ አላማ ማስረጃ እንዳይጠፋ ከማድረጉም በተጨማሪ ተጠርጣሪው በፈጸመው ወንጀል ምክንያት ለመበቀል የሚፈልጉ አካላት ካሉ እነዚህ አካላት ከሚያደርሱበት አደጋ ይጠበቃል፡፡

የጊዜ ቀጠሮ አሰጣጥና ርዝማኔ፡-

በወንጀል የተጠረጠረ አንድ ሰው በአርባ ስምንት ሰአት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለበት የኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገ-መንግስት የደነገገ በመሆኑ ፖሊስ የያዘውን ተጠርጣሪ በተባለው የጊዜ ገደብ ውስጥ አቅራቢያ ባለው ፍ/ቤት ማቅረብ አለበት፡፡ ልብ ልንለውና ከግምት ውስጥ ማስገባት ያለብን ነገር ተጠርጣሪውን ፍ/ቤት ለማቅረብ የሚወስደው ጊዜ በአርባ ስምንት ሰአት ውስጥ አይካተትም፡፡ በፍትሐ ብሔር ስነ ስርአት ህግ ቁጥር 29 እንደተቀመጠው ፖሊስ የያዘውን ተጠርጣሪ ፍርድ ቤት ካቀረበ በኋላ ፍርድ ቤቱም ተይዞ የቀረበውን ተጠርጣሪ በማረፊያ ቤት እንዲቆይ ወይም በዋስትና እንዲለቀቅ ውሳኔ መስጠት እንዳለበት በፍትሐ ብሔር ስነ ስርአት ህግ ቁጥር 59 ላይ ተቀምጦ ይገኛል፡፡

ፖሊስ በተጠርጣሪው ላይ የወንጀል ምርመራውን ካላጠናቀቀ ፍርድ ቤቱን በተጠርጣሪው ላይ የወንጀል ምርመራውን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው ይጠይቃል፤ ፍርድ ቤቱም የቀረበለትን የጊዜ ቀጠሮ የሚፈቅድ ከሆነ ይህን በመግለጽ በጽሁፍ ማሳወቅ አለበት፡፡ ፍ/ቤቱ ለሚሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ከአስራ አራት ቀን መብለጥ እንደሌለበት በስነ- ስርአት ሀጉ አንቀጽ 59 ላይ ተደንግጓ ይገኛል፡፡

የጊዜ ቀጠሮ አስፈላጊነት እና የዐቃቤ ህግና የፍርድ ቤት ሚና፡-

የጊዜ ቀጠሮ ዋና አላማውና አስፈላጊነቱ በምርመራ ወቅት ፖሊስ ማስረጃዎችን ለመሰብሰብ ሰፊ ጊዜ እንዲያገኝ ከማገዙም በላይ ማስረጃዎች እንዳይጠፉና እንዳይሰወሩ ያግዛል፡፡ በአብዛኛው በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች ወንጀሉን ስለመፈጸማቸው የሚመሰክሩባቸውን ሰዎች በጥቅምና በማታለል ማስረጃ እንዲጠፋ የሚያደርጉ በመሆኑና ምስክሮችንም በማስፈራራት እንዳይመሰክሩ የሚያደርጉ ስለሆነ የጊዜ ቀጠሮ እነዚህን ችግሮች ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡
በአብዛኛው የጊዜ ቀጠሮ ሲጠይቅ የሚታየው መርማሪ ፖሊስ ሲሆን ነገር ግን ዐቃቤ ህግ በተሰጠው ስልጣን መሰረት የምርመራ ዘርፉን የሚመራና የሚቆጣጠር ስለሆነ የጊዜ ቀጠሮ በሚጠየቅበት ወቅት ከፖሊስ ጋር በመነጋገር የተጠርጣሪን መብት በጠበቀ ሁኔታ የጊዜ ቀጠሮ እንዲጠየቅ ማድረግ ይኖርበታል፡፡

ዉድ ተከታዮቻችን በዛሬዉ ፅሁፋችን ስለ ጊዜ ቀጠሮ ምንነትና በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ግንዛቤያችሁን የሚያሳድግ መረጃ እንዳገኛችሁበት ያለንን እምነት እየገለፅን ማብራሪያ የሰጡንን ዐቃቤ ህግ አቶ አበበ ጌታሁንን በእናንተ በአንባቢዮቻችን ስም እጅግ አድርገን እናመሰግናለን

Address

Addis Ababa And Wolaytta S**o
Addis Ababa

Telephone

+251945956551

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ፍቃዱ ሞላ የህግ ቢሮ Fekadu Molla Law Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category