Desalegn Law Office

Desalegn Law Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Desalegn Law Office, Addis Ababa.

30/06/2025

ፍርሃት
(ደሱ ፍቅርኤል)

አህያሽ ልጅ ወልዶ...
"ስም አዉጣለት" ቢሉት 'ጅቦ' ብሎ ጠራዉ
ይህን እያዬ ነዉ ነገሽን ሲገምት ልቤ የሚፈራዉ።

እናትየ ሀገሬ...
አንድ ልጅሽ እዚህ - ለሰይጣን ተልዕኮ - ያ'ምላክ ስም ይጠራል
አንድ ልጅሽ እዚያ...
"ዝምታ ወርቅ ነዉ" ብሎ ለማሳመን ያለ ልክ ያወራል
የሚወድሽ ልቤ ዛሬያቸዉን አይቶ ነገሽን ይፈራል።

Desu Fikriel

...የኔ አባት መይሳው፣የንግሥና ድሎት....የቤተ-መንግሥት ወግ - ልቡን ሳያጓጓው - ነብሱን ሳያሳሳው፣ባዶ እግሩን ሄዶ ነው - ባዶ የነበረች - ሀገሩን ያነሳው።ታሪክ ምስክር ነው!በጠጅ መ...
22/06/2025

...የኔ አባት መይሳው፣
የንግሥና ድሎት....
የቤተ-መንግሥት ወግ - ልቡን ሳያጓጓው - ነብሱን ሳያሳሳው፣
ባዶ እግሩን ሄዶ ነው - ባዶ የነበረች - ሀገሩን ያነሳው።

ታሪክ ምስክር ነው!

በጠጅ መሳከር - ጮማ ስጋ መቁረጥ፣
ብርሃን የመሰሉ እንስቶች ማማረጥ፣
ሽቶ በጠገበ - የወይዛዝርት እቅፍ - ተከቦ መስለምለም፣
ሀር ዝምዝም ካባ - ለብሶ መንጎማለል - በወርቅ መሸለም፣
በካሳ ዘንድ የለም!

እንደ ተባ'ት አህያ - ፋንኖ ፋንኖ - ሁሉም በየፊናው፣
መሳፍንቱ ሁሉ - ቢከፋፈላትም - ሰፍሮ በየቁናው፣
ለቴዎድሮስ ግና...
የኢትዮጵያን አፈር - በጫማ መረገጥ - ሀጢያት ነው ለህሊናው።

የዓለም የጦርነት ዝግመተ ለውጥ እዚህ ደርሷል - እንደምታዩት። እኛ አፍሪካውያን በጠቅላላ፣ ኢትዮጵያውያን ደግሞ በተለይ የምንገኝበትን የአኗኗርና የአስተሳሰብ ደረጃ ደግሞ አስቡት። ያልጠፋነው...
16/06/2025

የዓለም የጦርነት ዝግመተ ለውጥ እዚህ ደርሷል - እንደምታዩት። እኛ አፍሪካውያን በጠቅላላ፣ ኢትዮጵያውያን ደግሞ በተለይ የምንገኝበትን የአኗኗርና የአስተሳሰብ ደረጃ ደግሞ አስቡት። ያልጠፋነው ኃይለኞች ስለሆንንና ሊያጠፉን ስላልቻሉ ነው ብለው የሚያስቡ የዋህ ኢትዮጵያውያን ዛሬም ድረስ አሉ። በእውነት እነዚህን ብርቅዬ አሳቢዎች በዓለም ገበያ አውጥተን መሸጥ ነበረብን። አይመስላችሁም?

ማንነቴን ሳሰላስለው(ደሳለኝ የኔአካል - ጠበቃና የሕግ አማካሪ)ፍልስፍና ከሚመረምራቸው ዋነኛ ጉዳዮቹ መካከል የሰው ልጅ መነሻ  ከየት ነው? መድረሻውስ (መጨረሻው (መጨረሻ ካለው)) ምንድነው...
08/03/2025

ማንነቴን ሳሰላስለው
(ደሳለኝ የኔአካል - ጠበቃና የሕግ አማካሪ)

ፍልስፍና ከሚመረምራቸው ዋነኛ ጉዳዮቹ መካከል የሰው ልጅ መነሻ ከየት ነው? መድረሻውስ (መጨረሻው (መጨረሻ ካለው)) ምንድነው? ዕጣ-ፋንታው ተወስኗል ወይስ አልተወሰነም? (ነፃ ፈቃድ አለው ወይስ የለውም?) ሰው ‘በልቡ እንዳሰበው’ ይኖራል ወይስ ሕይወቱን የሚዘውርለት ሌላ ‘አካል’ አለ? የልቡ ሃሳብስ ቢሆን የራሱ ነው ወይስ የሌላ? የሚሉት ጥያቄዎች የታላላቆቹ ፈላስፎች ጠረጴዛ ላይ ሲነሱና ሲወድቁ የኖሩ የመሟገቻ ሃሳቦች ነበሩ። አርስቶትል (Nicomachean ethics, book III)፣ ቅዱስ ኦገስቲን (City of God, book V, and On free choice of the will)፣ ቅዱስ ቶማስ አኩዊናስ (Summa theologica First Part Question 19, anf Question 83)፣ ሙሴ ማይሞኒደስ (the guide for the perplexed)፣ ስፒኖዛ (the ethics)፣ ሳርትር (being and nothingness)፣ ኒቼ (beyond good and evil)… ሌሎችም በርካቶች በእጃቸው ላይ የሚገኙትን ጠጠሮች በተለይ በነጻ ፈቃድ ጉዳይ ላይ ወርውረው አልፈዋል። ጉዳዩ ስለ ሰው ልጅ ነውና በአማኝም በኢ-አማኝም ዓይን ተመርምሯል። ከፈላስፋ ጀምሮ ከመነኩሴ እስከ ሳይንቲስት የምለው አለኝ ብለው በደረሱበት ልክ ሃሳባቸውን ገልጸዋል። የሰው ልጅ ነፃ ፈቃድ አለው፤ ዕጣ-ፋንታው አልተወሰነም የሚሉ፣ ዕጣ-ፋንታው ተወስኗል የሚሉ፣ ሁለቱ ሃሳቦች የሚታረቁ ናቸው የሚሉ እና እግዚአብሔር ነገሮች ከመሆናቸው በፊት ማወቁ ከነፃ ፈቃድ ጋር አይጋጭም የሚሉ ወዘተ አስተሳሰቦች ተነስተዋል። ያም ሆኖ የሰው ልጅ ምድር ላይ እስካለ ድረስ ጉዳዩ በየጊዜው እየተነሳ የሚመረመር እንጅ መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መዝገብ ቤት የሚመለስ አይደለም። በሀገራችንም ቢሆን የተለያዩ ሰዎች ነገሩ አሳስቧቸው አመለካከታቸውን በየስራዎቻቸው ላይ በቀጥታም በተዘዋዋሪም አስቀምጠው አልፈዋል። ድምጻዊ ይርጋ ዱባለ በአንድ ሙዚቃው ላይ
የሚሆን ይሆናል የማይሆን አይሆንም
ለቁጥቋጦ ያለው መቼም ዛፍ አይሆንም ይላል።
በዕውቀቱ ስዩምም ከይርጋ ጋር በሃሳብ እንደሚስማማ የሚያሳዩ ግጥሞች አሉት። ለምሳሌ ያህል ብቻ በስብስብ ግጥሞች መድበሉ ውስጥ የምትገኝ አንዲት ቁመተ-ዶሮ (አጭሬ ግጥም ቁመተ-ዶሮ እንዲሉ ሊቁ ኪዳነወልድ ክፍሌ) ግጥሙን እንጥቀስ።
እግዜርና ዳዊት በአንድ ተቧደኑ
ብቻውን ታጠቀ ጎልያድ ምስኪኑ
አንዳንዱ ተገዶ ለሽንፈት ሲፈጠር
በጥቅሻ ይወድቃል እንኳንስ በጠጠር። ይላል።
ይህን ሃሳብ የሚያጠናክር አስተሳሰብ በኤፍሬም ስዩም ስራ ውስጥም እናገኛለን።
…በተጻፈ ተውኔት
ባለቀ ዝግጅት
አሜን ማለት ከላይ መብረር
ለምን ማለት ክንፍን መስበር…
እያለ የሰው ልጅ ዕጣ ፋንታ ፅዋ ተርታ የተጻፈውን ተውኔት በስክሪፕቱ መሰረት መተወን ብቻ እንደሆነ አስረግጦ ይከራከራል። በርከት ያለው ሕዝባችንም ቢሆን (ጥናት የሚጠይቅ መሆኑ እንዳለ ሆኖ) አስተሳሰቡ የሰው ልጅ ዕድል አስቀድሞ ተወስኗል ወደ ሚለው ያደላል። ከፈጣሪው ጋር የሚጣላ ስለሚመስለው ነፃ ፈቃድ አለኝ እያለ ይሽኮረመማል እንጅ አኗኗሩ፣ ስነ-ቃሉም፣ ስነ-ግጥሙም ሲመረመር ግን ‘ለቁጥቋጦ ያለው መቼም ዛፍ አይሆንም’ የሚለውን አስተሳሰብ የሚያንጸባርቅ ነው።
ዕድሌ ነው እንጅ ከሰው ያሳነሰኝ
ብርቱካን ሲታደል ሎሚ የደረሰኝ እያለ ከእሱ ቁጥጥርና ፈቃድ ውጭ የሆነ ኃይል ሕይወቱ ላይ እንደሚወስን ይመሰክራል። ‘ይታደሉታል እንጅ አይታገሉትም’ ብሎ አጉል መፈራገጥ ትርፉ መላላጥ እንደሆነ ይናገራል። ‘የአርባ ቀን ዕድሌ ነው’ የሚለው አገላለጽም ቢሆን በሀገራችን የተለመደ መሆኑ እርግጥ ነው። ከእነዚህ የ’ተወስኗል’ አስተሳሰቦች በተቃራኒ የምናገኛቸው አሳቢዎች በአንጻሩ ጥቂት የሚባሉ ናቸው። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ለደሀነታችን ዋነኛው መንስኤ ይህ አስተሳሰባችን እንደሆነና ሊቀየርም እንደሚገባው ‘ኢትዮጵያዊነት ከየት ወዴት?’ በሚለው መጽሐፋቸው ላይ በስፋት ያብራራሉ። ይስማዕከ ወርቁ ደግሞ በአንድ ግጥሙ ላይ ጉዳዩን በጨረፍታ ነክቶት ያልፋል።
የተኛ በቆሎ ጎርፍ የደፈጠጠው
ተኝቶም ያፈራል ትል እያላመጠው
ድንጋዩን ሳይጫን አፈሩን ሳይለብሰው
መፈርጠጡስ ይቅር መዳህ ያቅተዋል ሰው?
ሰው አፈር እስካልለበሰ፡ ክንዱን እስካልተንተራሰ ድረስ ሕይወቱን በትግሉ የመለወጥ ኃላፊነት እጁ ላይ እንደሆነና ይህን ለማድረግም ነጻ ፈቃድ እንዳለው በተዘዋዋሪም ቢሆን ይጠቁማል።
የነጻ ፈቃድ ጉዳይ እንግዲህ ማንነታችንን ስናሰላስል አስቀድመው ከሚመጡልን ግዙፍ ጥያቄዎች አንዱ ሲሆን ከዚህ ግዝፈት በታች የሆኑ ሌሎች ንዑስ ጥያቄዎች ደግሞ አሉ። (ንዑስ የተባሉት ከዕጣ-ፋንታ ጥያቄ ግዝፈት አንፃር ሲታዩ እንጅ ራሳቸውን አስችለን ነጥለን ስንመለከታቸው ግን በየራሳቸው እጅግ ግዙፍና ውስብስብ ናቸው) ከእነዚህ ‘ንዑስ’ ጥያቄዎች አንፃር የነጻ ፈቃድ መኖር አለመኖር ላይ መከራከር ቅብጠት ነው። ለጊዜው ዕጣ-ፋንታችን ተወስኗል የሚለውን ጥለን፤ ነጻ ፈቃድ አለን የሚለውን አንጠልጥለን ብንቀጥል እንኳ አሁን ‘እኔ’ የምንለው ማንነታችን በእርግጥም በነጻ ፈቃዳችን የመረጥነው እውነተኛው ‘እኔነት’ ነው ወይስ በሌሎች ሰዎችና በማኅበረሰባችን ተጽዕኖ የተፈጠረ ሀሰተኛ ማንነት ነው? የሚለው ከእያንዳንዳችን ፊት የቆመ ጥያቄ ነው። መነሻው የትም ይሁን ሕይወት መንገድ ነው። ከእናታችን ማህፀን ከወጣንባት ቅፅበት ጀምሮ (ምናልባት ከዚያም በፊት ጀምሮ) በዚህ መንገድ ላይ ተገኝተናል። መንገዱ በአሳባሪዎች የተሞላ እንደመሆኑ መጠን (በመረጥነው) አሳባሪ ስንጓዝ አረማመዳችን ራሳችንን ይመስላል ወይ? መስለን የምንታየውና በትክክልም የሆንነው ማንነታችን አንድ አይነት ናቸው ወይስ እንደ ልብሶቻችን የክት እና የአዘቦት ‘ማንነት’ አለን? ፈጣሪ (ወይም ተፈጥሮ) ዕጣ-ፋንታችንን ወስኗል ወይም አልወሰነም ከማለታችን በፊት የእኛ ዕጣ-ፋንታና ነጻ ፈቃድ ማኅበረሰቡ በሰራው ቅርጽ (ሞልድ) ውስጥ ገብቶ አልተጨፈለቀም ወይ? ከላይ ከተብራራው የነጻ ፈቃድ ጉዳይ ይልቅ ይህኛው ጥያቄ ለሰው ልጅ የበለጠ ተግባራዊ ጠቀሜታ ያለው ይመስላል። ወደ ሰማይ ከማንጋጠጣችን በፊት መጀመሪያ የጎንዮሹ ምን ይመስላል የሚለውን መመርመር አስፈላጊ ነው። ፈጣሪ ነጻ ፈቃድ ሰጥቶን ከሆነ እኛስ በተሰጠን ነጻ ፈቃድ ልክ በነፃ ምርጫችን እየኖርን ነው ወይ? ማኅበረሰባዊ ድጋፍ (Social approval) ለማግኘት ስንል የማንመርጠውን አልመረጥንም? የማንፈልገውን አልሆንም? የምንጠላውን የምንወደው አልመሰልንም? ራሳችንን እየኖርን ነው ወይስ የሆነ ሰውን እየተወንን? የሕይወታችን ደራሲዎች ነን ወይስ ማኅበረሰብ የጻፈልንን የማንነት መነባንብ አነብናቢዎች? ከዋነኛው የዕጣ-ፋንታ ክርክር በፊት ይህን ጥያቄ ማንሳት የሚያስፈልገው ሞኝ ላለመሆን ነው። ፈጣሪ በፈቀድነው መንገድ እንድንኖር ቢፈቅድልንም ፈቃዳችንን ካልኖርነው እኛ ላይ ያለው ነጻ ፈቃድ ‘መቃብር ላይ እንደተቀመጠ ጣፋጭ ምግብ’ መሆኑ እርግጥ ነው። መኖሩም አለመኖሩም ትርጉም አይሰጥም። ወደ ውሃው ወይም ወደ እሳቱ እጃችንን የመስደድ ምርጫ ቢሰጠንም እንኳ እጃችንን የምንሰደው ወደፈለግነው ሳይሆን ማህበረሰብ (ወይ ሰዎች) እንድንሰድበት ወደሚፈልጉት ከሆነ የተሰጠንን ነፃ ፈቃድ አክስረናል። በዚህም የተነሳ ሕይወትን አክስረናል፤ አርክሰናልም። ይህ እንግዲህ እንደ አለመታደል ሆኖ የአብዛኞቻችን የዕለት ተዕለት የአኗኗር ዘዬ ነው። ከእውነተኛው ማንነታችን ጋር ተካክደን ለወል ፍላጎት እጅ ሰጥተናል። የግል እውነታችንን ለመንጋው ፍላጎት ባርያ አድርገናታል። ለጥፊ የዘረጋነውን እጅ (በይሉኝታ ወይም በማስመሰል የተነሳ) ሃሳባችንን ቀይረን አጨብጭበንበታል። ሰዎች ሲወዱት አይተን፡ የማንፈልገውን ተምረናል። የሚያስመልሰንን በልተናል። ጥሩ ሰው መሆናችንን ለማረጋገጥ የማኅበረሰቡን ‘የጥሩ ሰውነት መስፈርት’ ሸምድደን ተውነናል። ኤርቪንግ ጎፍማን የተባለ የማኅበረሰብ አጥኚ እኤአ በ1959 the presentation of self in everyday life በሚል ርዕስ ባሳተመው ጥናቱ የእያንዳንዳችን የየዕለት ግንኙነት (daily interaction) ትወና መሆኑን ያስረግጣል። ግላዊ ማንነታችንን ትተን ማኅበረሰቡ እንድንሆን የሚጠብቅብንን ማንነት ስናሳድድና እሱኑ ስንተውን ከእውነተኛው እኛነታችን ጋር እንተላለፋለን። አስቀድሞ ከተሰራው ቅርጽ ጋር እንድንገጥም ሲባል ራሳችን በራሳችን ከርክመን ከርክመን ሌላ ሆነን እናርፈዋለን። ለመመሳሰል ስንል ልዩነታችንን በህዝብ ቀለም እንደልዛለን። ባዶ እጁን የቆመ ማኅበረሰብ መሐል ስለተገኘን ብቻ አንዳች ነገር ይዘን መወለዳችን ኃጢአት መስሎ ይታየንና የያዝነውን ደፍተን ከባዶው መሐል ባዷችንን ገብተን እኩል እንሆናለን። ከዚያ በኋላ የሚኖረን እድል (ያውም ከነቃን) “እንዲህ ነበርኩ እንዴ?” ብለን መጠየቅ ነው። ፈጣሪም ገና ሲያየን በሚላን ኩንዴራ አገላለጽ “እሱ ነው፤ ግን እሱን አይመስልም” ብሎን ያልፋል። ሕይወታችን ይህ ከሆነ ነጻ ፈቃድ ኖረ አልኖረ ፋይዳው ምንድነው?

በሰይጣኒዝም ተጠረጠርነ😊ተመስገን ነው መቼም😋
01/12/2024

በሰይጣኒዝም ተጠረጠርነ😊
ተመስገን ነው መቼም😋

ልክ ልወድቅ ስል...(ደሱ ፍቅርኤል)ትንሽ ልጅ ነበርኩ። 14 ዓመቴ ቢሆንም በቀጥታ ከ1ኛ ክፍል ስለጀመርኩ 9ኛ ክፍል ደርሻለሁ። ቅርጽ ያለው ህልም አልነበረኝም። አንድም መጽሐፍ አንብቤ አላ...
24/09/2024

ልክ ልወድቅ ስል...
(ደሱ ፍቅርኤል)

ትንሽ ልጅ ነበርኩ። 14 ዓመቴ ቢሆንም በቀጥታ ከ1ኛ ክፍል ስለጀመርኩ 9ኛ ክፍል ደርሻለሁ። ቅርጽ ያለው ህልም አልነበረኝም። አንድም መጽሐፍ አንብቤ አላውቅም። ማንበብ እንዳለብኝ የነገረኝ ሰውም አልነበረም። ልብወለድና የግጥም መድበል የሚባሉ ነገሮች ባዳዎቼ ነበሩ። (አባቴ ግጥም ስለሚፅፍ የእሱን ግጥሞች ተከትዬ ስለቅንጅት መሪዎች በወሬ የሰማሁትን ስለ ልደቱ፣ ስለ ኃይሉ ሻወል፣ ስለ ብርሃኑ ነጋ ወዘተ ስማቸውን ሰምና ወርቅ እያደረግኩ ግጥም ብጽፍም ወደፊት ገጣሚ እሆናለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም። ገጣሚ የሚባል ነገር እንዳለም አላውቅም) ማትሪክን በጣም ፈርቼው ነበር (ምክንያቱም የ9ኛ ክፍል መጀመሪያ ወሰነ-ትምህርት ውጤቴ ያስደነግጣል።) 9ኛ ክፍል የመጀመርያው ወሰነ ትምህርት ሲያልቅ ግን ነገር ተቀየሩ። አጎቴ Zemene Habtu እኔንና ሌሎች ህልም አልባ ውሪዎቹን ሰብስቦ ረዥሙ ራዕይ የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች ማህበርን መሠረተ። (ስሜ ለመጀመርያ ጊዜ በኮምፒውተር ተጽፎ ሳዬው ኡፍፍፍፍፍ የተሰማኝ ደስታ)። (ራዕይ የሚባል ነገር እንዳለ ያስተማረኝና በሌላ መንገድ የመራኝ አጎቴ ዘመነ ነው።) ማህበራችንን በመሰረትን በወሩ? ይመስለኛል አጎቴ በምስሉ ለምትመለከቱት ሰው (ለኃይለማርያም ኤፍሬም) (ከተማው በሙሉ ኃይልሽ ብሎ ነው የሚጠራው) የትብብር ደብዳቤ ጻፈ - ለማህበራችን ልጆች በነጻ የእንግሊዝኛ ቋንቋ እንዲያስተምርልን የሚል። ኃይልሽ ሁለት ልጆችን ለማስተማር ፈቃደኛ ሲሆንልን አኔና ያደል የሚባል ልጅ ተመርጠን ኢንፎቴይንመንት የቋንቋ ትምህርት ቤት ገባን። ኃይልሽ የቋንቋ ችሎታዬን ብቻ ሳይሆን ህልሜንና ዓለምን የምረዳበትን መንገድ አሳደገልኝ። የክፍል ደረጃዬ በሚያስደንቅ ፍጥነት ተሻሽሎ የ10ኛ ክፍል ማትሪክንም በከፍተኛ ውጤት በንቀት አለፍኩት። ልብ ወለድ (የመጀመሪያዬ ሮሜዎና ዡልየት፣ ቀጥሎ አልወለድም እያለ...) ማንበብ ጀመርኩ። ከልብወለድም በላይ ከትምህርቴም ከዕድሜዬም የላቁ እንደ political science and international relations አይነት ዘርፎች ላይ ሳይቀር ግብብዳ መጻሕፍትን ማጣጣም ጀመርኩ። የተቀረጸ ህልም ኖረኝ። መጻሕፍት ማሳተም እንደሚቻል አወቅኩ። ዓለም ከጎንደር እንደሚሰፋ ተገነዘብኩ። አልኮል መጠጣትን የሚከለክለውን ቤተሰባዊ አቋም እንዳጸና ረዳኝ (አሁን በዓመት አንዴ ወይ ሁለቴ ብቻ ግማሽ ጠርሙስ ቢራ ወይም አንድ ብርጭቆ ወይን ወይም ጠጅ እጠጣለሁ። እስከዛሬ ድረስ ብዙ በመጠጣት ሪከርድ የያዝኩት ሀገሬን ሰቀሏትን አሳትሜ ጓደኞቼ ያከበሩልኝ ቀን ሶስት ቢራ በመጠጣት ነው። ተንገዳግጃለሁ😂።) ኃይልሽ ህይወቴ ውስጥ ባይኖር ኖሮስ? ብዬ ሳስብ እደነግጣለሁ። ቁጥብነቱና ትጋቱ ያስደንቀኛል። ይህ ሰው ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለከተማችን ብዙ ልጆች (እስካሁንም ድረስ) ህልም፣ ቋንቋና ባህል ያስተምራል። ከቋንቋ መምህርነቱና አስጎብኝነቱ ባሻገር 16 መፃህፍትን አሳትሞ ለንባብ አብቅቷል። አብዛኞቹ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያዎችና የቱሪዝም መጻሕፍት ናቸው። ከስር በፎቶ የምትመለከቱት 'ድብ አንበሳ' መጽሐፍ ደግሞ በኢንሳይክሎፔዲያ ስልት የተጻፈ ድንቅ የምርምር ስራው ነው። ሰሞኑን በድጋሜ በcolor print ታትሞ በጃፋርና በእነሆ መጻሕፍት ቤቶች እየተሸጠ ይገኛል። አንብባችሁ እንደምትወዱት አውቃለሁ። Teogon Teogon ኃይልሽ ለሰጠኸኝ ሁሉ አመሰግናለሁ።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Desalegn Law Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share