19/05/2025
ሰበርርርርርርርርርርርር
አማኑኤል ሞላ የተባለ የፀረ ሰላሙ ሃይል ከፍተኛ መሪ እጁን በሰላም ለመከላከያ ሰራዊቱ ሰጥቷል!
የዘመነ ካሴ ቀኝ እጅ የነበረው አማኑኤል ሞላ የሽብር እንቅስቃሴው በቃኝ በማለት በሰላም እጁን ለጀግናው ሰራዊታችን ሰጥቷል፡፡ አማኑኤል በቡድኑ ውስጥ የሚስተዋለው ፅንፍ የረገጠ ጎጠኝነት ከሚባለው በላይ ተስፋ በማስቆረጡ ይህን ውሳኔ እንደወሰነም መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በቡድኑ ውስጥ ለረዥም ጊዜ ሰፍኖ የቆየው የጥቅም እና የስልጣን ሽኩቻ አሁን ላይ በአደገኛ ሁኔታ ወሎ፣ ጎንደር፣ ጎጃም እና ሸዋ ወደሚል ጎጠኝነት አድጎ የቡድኑ መሪዎች ጎራቸውን ለይተው እርስ በርስ በውጊያ ላይ እንደሆኑም ይታወቃል፡፡ ይህ የአማራን ህዝብ የሚያከፋፍል ብቻ ሳይሆን ደ*ም የሚያቃባ መሆኑን ጭምር የተረዱት ብልሆች እጃቸውን በሰላም በመስጠት ላይ ናቸው፡፡
የዘመነ አሽከሮች አንድነት ተፈጠረ ብለው ገና ዘለው ሳይጠግቡ ቡድኑ መናድ ጀምሯል😃 የሚገርመው እጅ እየሰጡ ያሉት ቡድኑ አሉኝ የሚላቸው ናቸው፡፡ ይህም ቡድኑ እንዳበቃለት በቂ ማሳያ ነው!