28/08/2026
በመደበኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ታገዱ!
የማህበራችን ብርሃን ባንክ ሠራተኞች ማህበር ነባር ማህተም እያለ ፤ ከማህበራችን ዕዉቅና እና አሠራር ዉጪ ( የኢ.ፌ.ድ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀፅ 364 እንዲሁም ያልታተመዉ የሰ/መ/ቁ 145996) ስድስት ግለሰቦች አዲስ ማህተም በማስቀረፅ በማህበራችን ስም በመንቀሳቀሳቸው እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ የአሠሪና ሠራተኛ ወሳኝ ቦርድ በመ/ቁ 053/3/17 እና 034/1/17 ሲታዩ የነበሩ ወደ 3,000 የሚጠጉ ሠራተኞችን የሚመለከተው ከጥር/2015 እስከ ሐምሌ/2017 ድረስ የቤት አበል ዉዝፍ ክፍያ ክርክር ጉዳይ "....ለሠራተኛው ተፈፅሟል ፤ በስምምነት ተፈቷል...." በማለት የክስ መዝገቡ በሚገርም ሁኔታ በነሐሴ 08/2018 ለማዘጋት ጭምር ችለዋል።
ማህበራችን የእነዚህ ግለሰቦች ተግባር በተመለከተ ሙሉ ማጣሪያ አድርጎ እና ማስረጃ አደራጅቶ ክስ እስኪመሰርት ድረስ የቅድመ ክስ የእግድ ትዕዛዝ (የፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.154/2 እንዲሁም በቅፅ 25 የታተመዉ የሰ/መ/ቁ.191402) እንዲሰጥለት ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በፅሁፍ አቤቱታ ጠይቋል።
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አቤቱታችን ተመልክቶ እነዚህ ግለሰቦች ከነሐሴ 20/2018 ጀምሮ የብርሃን ባንክ ሠራተኞች ማህበርን በመወከል ማንኛውም ተግባር እንዳይፈፅሙ ፣ አዲስ ያስቀረፁት ማህተም እንዳይገለገሉ ጊዜያዊ የእግድ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ግለሰቦቹ የግል ፍላጎታቸው ለማሳካት ከማህበራችንም ሆነ አባል ሠራተኛዉ ዕዉቅና ዉጪ የፈፀሙት ዝርዝር ተግባር በተመለከተ ዉጤቱን በቀጣይ ጊዜ የምናሳዉቃችሁ ይሆናል። ህጋዊ ዉክልና ሳይኖር የተፈፀመ ተግባር ሁሉ እንዳልተደረገ የሚቆጠር በመሆኑ ጉዳዩን በትጋት ተከታትለን የምናሳዉቃችሁ ይሆናል።
የብርሃን ባንክ ሠራተኞች ማህበር
ለባንኩ እና ለሠራተኛው የጋራ ተጠቃሚነት እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ሠላም የሚተጋ የሠራተኛው እዉነተኛ ማህበር ፤ የዘወትር ድምፅ!
ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም.