Kidus Asnake Law office

Kidus Asnake Law office Kidus Asnake Law Office

01/10/2022

የጠበቃ ቀልዶች
ሰጥቶ መቀበል
ጠበቃ፤ ሐኪምና የባንክ ሰራተኛ በሞት የተለያቸውን ወዳጃቸውን ሊቀብሩ ከአስከሬኑ አጠገብ ቆመዋል፡፡ በሀዘናቸው መሐል የባንክ ሰራተኛው “በኛ ባህል መሠረት ሟች ለሰማይ ቤት የሚሆነው ትንሽ ገንዘብ መስጠት ልማዳችን ነው፡፡ ስለዚህም ለምን የተቻለንን አንረዳውም?” ሲል ሓሳብ ያቀርባል፡፡ በሓሳቡ ሁሉም በደስታ ተስማምተው መጀመሪያ የባንክ ሰራተኛው ከኪሱ ድፍን መቶ ብር አውጥቶ የሬሳ ሳጥኑ ስር ሸጎጥ አደረገ፡፡ ሐኪሙም እንደዚሁ ድፍን መቶ ብር ለገሰ፡፡ በመጨረሻም ጠበቃው ሁለቱም የሰጡትን 200 ብር ሰብስቦ ኪሱ ከከተተ በኋላ የሶስት መቶ ብር ቼክ ጽፎ ሳጥኑ ስር በመክተት ‘የቻለውን ያህል’ ረድቷል

10/09/2022

እንኳን ከዘመን ወደ አዲስ ዘመን አሸጋገረን! አዲሱ አመት የጤና የብልጽግና እንዲሁም የብዙ ታላላቅ ድሎችን የምንጎናጸፍበት እንደሆነ እምነቴ የፀና ነው
🌻ምርጥ ዋዜማ ተመኘሁ 😊🌻
ቅዱስ አስናቀ በዛብህ
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ
የእናንተው ምርጥ ጓደኛ 🙏🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

ታሪክ ይቀየራል !

ህልም የሚመስሉ እደርስባቸዋለው ተብለው የማይታሰቡ ነገሮች በሙሉ እውን ይሆናሉ ፤ አይሳኩም የሚባሉ ሁሉ ተሳክተው ይገኛሉ ፣ በህልማችን እንኳን ይሆንልናን ብለን ያላሰብናቸውን ነገሮች ሆነውልን አይተናል! እና ለፈጣሪ ምን ይሳነዋል! ቀና እና ዝግጁ አድርገን ከጠበቅነው የፈለግነውን ቢደረግልን ብለን አብዝተን የተመኘነውን ነገር በደንብ አድርጎ ይሰጠናል! አስታውሱ በእስከዛሬ ህይወታችን ስንት ድንቅ ተዓምር አይተናል? ስለዚህ ተዓምራቱ ይቀጥላል!

🌻️🙏🙏🌼🌼🌼🎀🎀🎀🎀🎀💝💝💝💝💝💋❤️💖💋❤️💞🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻😍🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼💋💋💋💋💋🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

07/09/2022

እናትና አባቱን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በመግደሉ በከባድ የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ የተባለ ተከሳሽ የቅጣት ማቅለያ ካለው እንዲያስመዘግብ ዕድል ተሰጠው፡፡ ተከሳሹም “የሙት ልጅ ነኝ! ይታይልኝ” በማለት አይኑን በጨው ታጥቦ ቅጣት እንዲቀልለት ተማጽኗል፡፡

25/08/2022

ዋስትና መብት(የ-)

ይመለከቷል: ተከሳሽን የሚጠቅም ቅጣት

• በወንጀል የተከሰሰ ሰው የዋስትና ማረጋገጫ በማቅረብ ከውጭ ሆኖ ለመከራከር ያለው ሀገ-መንግስታዊ መብት

የዋስትና መብት በሕገ መንግስት ጥበቃ ከተደረጉት የተያዙ ሰዎች መሰረታዊ መብቶች አንዱ ነው፡፡ የኢ.ፌ.ዲ. ረፑብሉክ ሕገ መንግስት በአንቀጽ 19(6) ስር የተያዙ ሰዎች በዋስትና የመፈታት መብት ያላቸው መሆኑን በመርህ ደረጃ ያስቀመጠ ሲሆን ይህ በህገ መንግስቱ የተከበረው መብት ሊነፈግ፣ ሊገደብ ወይም በቂ የሆነ የዋስትና ማረጋገጫ እንዲቀርብ ሊደረግ የሚችለውም አግባብነት ባላቸው ሌሎች ዝርዝር ሕጎች መሰረት በልዩ ሁኔታ ስለመሆኑ ይኸው የሕገ መንግስቱ ድንጋጌ በግልፅ ያሳያል፡፡ በመሆኑም የዋስትና መብት መሰረታዊ የሆነ ሕገ መንግስታዊ መብት ቢሆንም ፍፁም መብት ሳይሆን በሕጉ አግባብ ሊነፈግ ወይም ሊገደብ የሚችል ነው፡፡ ስለሆነም የዋስትናው ጥያቄ ተቀባይነት አለው? ወይስ የለውም? የሚለው ላይ ውሳኔ የሚሰጠው ፍርድ ቤት እንደመሆኑ መጠን በዚህ ረገድ አግባብነት ያለውን ልዩ ሕግ መሰረት አድርጎ ጉዳዩን ሊመዝነውና ተገቢውን ውሳኔ ሊሰጥበት የሚገባው ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው፡፡

የወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁጥር 67(ሀ) ድንጋጌ ሲታይ በዋስትናው ወረቀት የተመለከቱትን ግዴታዎች አመልካቹ የሚፈጽም የማይመስል የሆነ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በዋስትና ወረቀት የመለቀቅ ማመልከቻውን መቀበል እንደማይችል ሲደነግግ በወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 67(ሐ) ስር የተመለከተውና የዋስትና ወረቀቱን ላለመቀበል ምክንያት የሚሆነው ነገር ደግሞ አመልካቹ ምስክሮችን በመግዛት (በማባበል) ወይም አስረጂ የሚሆኑበትን ያጠፋ ይሆናል ተብሎ የሚገመትበት ሁኔታ መኖሩ ነው፡፡ እነዚህ ድንጋጌዎች ይዘታቸው ሲታይ ፍርድ ቤቱ ግምት ለመውሰድ በሕጉ ስልጣን የተሰጠው መሆኑን ያስገነዝባሉ፡፡

እዚህ ላይ ሊስተዋል የሚገባው ዋናው ጉዳይ ድንጋጌውን በመተግበር ረገድ ፍርድ ቤቱ ግንዛቤ /ግምት/ ውስጥ ሊያስገባው የሚገባው ምክንያት ምንድነው? የሚለው ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ዋስትናውን ለመከልከል ግምቱን መነሻ የሚያደርግባቸው ሁኔታዎች በተጠቀሰው ድንጋጌ በግልፅ አልተመለከቱም፡፡ እንዲህ ከሆነ አንድ ተከሳሽ የዋስትና መብት ቢከበርለት ግዴታውን የሚፈፅም የማይመስል ነው፣ ማስረጃም ሊያጠፋ ይችላል ተብሎ ግምት የሚወስደው በቂና እና ሕጋዊ ሊባሉ በሚችሉ ምክንያቶች ሊሆን ይገባል ተብሎ የሚታመን ሲሆን ምክንያቶች በቂና ሕጋዊ ናቸው የሚለው ጉዳይ ከተለያዩ ከባቢያዊ ሁኔታዎችና ከጉዳዩ ልዩ ባህርይ አንፃር እየታየ ፍርድ ቤቱ ግንዛቤ ሊወስድባቸው የሚችላቸው ነጥቦች ናቸው ተብሎ የሚታሰብ እንጂ ቁርጥ ያለ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ የሚቻልባቸው ሁኔታዎች አሉ ለማለት የማይቻልበት ጉዳይ ነው፡፡ ስለሆነም የወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 67 በጠቅላላው ሲታይ ፍርድ ቤት የዋስትና መብትን የሚነፍግባቸውን ሁኔታዎች የሚያሳይ ሲሆን ምክንያቶቹን ፍርድ ቤቱ ከተለያዩ ሁኔታዎች በመመልከት ሊመዝናቸው የሚገባቸው ሲሆን የድንጋጌው ቅርጽ፣ ይዘትና መንፈስ ሲታይ በሁኔታዎቹ ግምት የመወሰድ ያለመውሰድ ጉዳይ ፍርድ ቤት ስልጣን (Discretion) ያለው መሆኑን ያሳያል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 67874 ቅጽ 13

20/08/2022

Address

Addis Ababa

Telephone

+251955424370

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kidus Asnake Law office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share