07/06/2026
የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በአርሲ ምድር በተፈጸመው ጥቃት ላይ ፍትህ ጠየቁ!
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን አህጉረ ስብከት ስር በሚገኙት የአሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በንጹሐን ምዕመናንና በቤተ ክርስቲያናት ላይ ተፈጽሟል የተባለውን ጥቃት በመቃወም ምዕመናን፣ ወጣቶች እና የማኅበረሰብ ክፍሎች ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ፍትህ እየጠየቁ መሆኑ ተገልጿል።
በተመሳሳይ ምዕመናንና ወጣቶች “እኛ የአቡነ ጴጥሮስ ልጆች ነን፤ የአባቶቻችንን ሃይማኖት በጽናት እንጠብቃለን” በማለት ለተጎዱ ወገኖች ፍትህ እንዲሰጥ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል።
#አርሲ #ኢትዮጵያ